የኢየሱስ ክርስቶስ እንግልት ለሰው ልጆች መዳን

የእየሱስ ክርስቶስ ስቅለት


ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን የእዳ ደብዳቤ ይቀድ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅነታቸውን በደሙ ያጸና ዘንድ በእለተ አርብ የደረሰበትን መንገላታት በአጭሩ ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍን ገለጥ አድርገን እንመልከት ፡- (ማቴ. 27÷27-31)
👉 ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ ለሊቱን ከ12ቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ በኾነው በይሁዳ መሪነት ታግዘው ከያዙት በኃላ እያንገላቱት ወደ ሐና ወሰዱት፡፡
👉 ሐና ከፊት እየመራ እየደበደቡ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀያፋ ቀጥሎም ወደ ጲላጦስ ወሰዱት፡፡
👉 ከጲላጦስ ወደ ወደ ሔሮድስ በማመላለስ እንዲንገላታ ተደርጓል፡፡
👉 በሂደቱም እየሰደቡትና እየዛቱበት ፊቱን በጥፊ ራሱን ደግሞ በዱላ ይመቱ አሰቃይተውታል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰውልጆች ነጻ መውጣት ሲል በዕለተ ዓርብ ከሦስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት የተቀበላቸው መከራዎች በጥቂቱ ስንቃኝ፡-
👉 በጅራፍ ተገርፎአል፡፡
👉 መስቀሉን ተሸክሞ በቀራንዮ ተራራ እየወደቀ እየተነሣ ተጉዟል፡፡
👉 የገዢው የጲላጦስ ወታደሮችም እያዳፉት፣ ርኩስ ምራቃቸውንም እየተፉበትና እያፌዙበት ወደ ተራራው እንዲወጣ ተደርጎአል፡፡
👉 የነቢያት ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ልብሱን ገፈው ከለሜዳ አልበሰውታል፡፡
👉 በልብሱም ላይ ዕጣ ተጣጥለው ተካፍለውታል፡፡
👉 የእሾህ አክሊል ጉንጉን በራሱ ላይ በማድረግ የሰማይና የምድር ንጉሥ እያሉ ተሳልቀዋል፡፡
👉 ጎኑን በጦር ወግተውታል፡፡
👉 እጆቹን እና እግሮቹን በ5 ችንካሮች ቸንክረው በመስቀል ላይ ሰቅለውታል፡፡
በመስቀል ላይ እያለ ከተናገራቸው ውስጥ፡-
👉 እየበደሉት እሱ ግን ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው›› ይል ነበር፡፡
👉 ‹‹እነሆ ሁሉም ነገር ተፈጸመ››
የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ፈሪሳውያን በክርስቶስ ላይ ያቀረቡት መሠረተ ቢስ ክስና ውንጀላ፡-
👉 ለቄሳር ግብር መክፈል አይገባም በማለት አስተምሮል፡፡
👉 ዕለተ ሰንበትን ሽሮአል፡፡
👉 ራሱንም ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሏል የሚሉ ናቸው፡፡
የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ፈሪሳውያን በክርስቶስ ላይ ያቀረቡትን መሠረተ ቢስ ክስና ውንጀላ ለማጽናት የሄዱበት እርቀት፡-
👉 በሐሰት የሚመሰክሩ ምስክሮችን በገንዘብ አባብለውና አደራጅተው አስመሰከሩ፡
👉 በርባን የተባለው ወንጀለኛ እንዲፈታ ንጹኸ ባሕሪ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን እንዲሰቅለው ገዥው ጲላጦስ ልመና አቅርበዋል፡፡
👉 የገዥው ጲላጦስ ባለቤት በሕልም ተረድታ እጁን በጻድቅና ንጹሕ ሰው ደም እንዳያስገባ ስለመከረችው ‹‹እኔ ከዚህ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ›› በማለት እጁን ከታጠበ በኋላ አሳልፎ ሰጣቸው፡፡
👉 ገዥው ጲላጦስ ንጹህ መኾኑን እያወቀ ወንበሩን ለማጽናት በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጦ የሰጠው የተዛባ ፍርድ ለትምህርት ይኾን ዘንድ ሲታወስ ይኖራል፡፡
👉 የኢየሱስ የስቅለት ውጣ ውረድ ለእውነት መቆምን፣ ከተዛባ ፍርድ መቆጠብን፣ ከሐሰት ምስክርነት ራሰን መጠበቅን፣ እስከመጨረሻው መጽናትን፣ ምልጃን፣ እስከሞት የሚያደርስ ፍቅርን እንማርበት ዘንድ እነኾ አብነት ኾኖ ዛሬም ዘልቋል፡፡

Discover more from Mahidere Tsibeb

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading

Design a site like this with WordPress.com
Get started