አርሰናል አሌክሳንደር ዚንቼንኮን ማስፈረማቸውን ይፋ አደረጉ !

አሌክሳንደር ዚንቼንኮን

አርሰናል የ 25 ዓመቱን የኋላ መስመር ተጫዋች አሌክሳንደር ዚንቼንኮን ከማንችስተር ሲቲ ማስፈረማቸው ይፋ ሆኗል ።

ለዝውውሩ ወደ ሰላሳ ሁለት ሚልዮን ዩሮ ወጪ እንደሆነ ሲገለፅ ቀድሞ በሲቲ ቤት ከሚያውቀው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ጋር ዳግመኛ አብሮ የመስራት ዕድልንም አግኝቷል ።

የሀያ አምስት አመቱ ዚንቼንኮ በዚህ ሳምንት ሁለት የጤና ምርመራዎችን አድርጎ በተሳካ ሁኔታ ሲያልፍ የሚቀጥሉትን አራት አመታት በአርሰናል የሚያቆየውን ውል እንደተፈራረመ ተገልጿል ።

ዚንቼንኮ በተከላካይ መስመር እንዲሁም በመሀል ሜዳ ስፍራ ላይ መጫወት የሚያስችል ብቃት ያለው ተጫዋች መሆኑ ይታወቃል ።

ዚንቼንኮ በማንቸስተር ሲቲ ፕሪሚየር ሊጉን እና ካራባኦ ዋንጫን አራት አራት ጊዜ ሲያነሳ አንድ ጊዜ ደሞ የኤፌ ኤ ካፕ ዋንጫን አሳክቷል ።

መድፈኞቹ ከዚህ ቀደም ከማንችስተር ሲቲ አጥቂውን ጋብርኤል ጄሱስን ማስፈረማቸው ይታወሳል ።

መድፈኞቹ በዝውውር መስኮቱ አስቀድሞ ጋብሬል ጄሱስ ፣ ማርኪኖህስ ማት ተርነር እና ፋቢዮ ቬራ ማስፈረማቸው የሚታወስ ነው ።

አርቴታ እና አሌክሳንደር ዚንቼንኮ

የልጅነት ህልሜ እውን ሆኗል “

የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አሌክሳንደር ዚንቼንኮ መድፈኞቹን መቀላቀሉ ደስተኛ እንዳደረገው በሰጠው አስተያየት ተደምጧል ።

” የቡድን ስብስቡን ስለተቀላቀለ ደስ ብሎኛል አሌክስን ከዚህም በፊት በደንብ አውቀዋለሁ ፣ ከሲቲ ከተለያየሁ በኋላም ስፈልገው ነበር ጥሩ ብቃት ያለው ተጫዋች ሲሆን ለቡድናችን ጥራትን ይጨምራል ።

በተለያዩ ስፍራዎች መጫወት መቻሉ ለቡድኑ የማጥቃትም ሆነ የመከላከል ስራ እንደሚያግዘን አምናለሁ ፣ እንደ ግለሰብም አሌክስ ጥሩ ስብዕና ያለው ተጫዋች ነው ” ሲል አርቴታ ሀሳቡን አካፍሏል ።

ዚንቼንኮ በበኩሉ ” በመጀመርያ የልጅነት ህልሜ እውን ሆኗል ፣ ልጅ እያለሁ የአርሰናል ደጋፊ ነበርኩ በተለይ ቴሪ ሄንሪ እና ወጣቱ ሴስክ ፋብሪጋስ ሲጫወቱ ማየት ያስደስተኝ ነበር ” ሲል ተደምጧል ።

Discover more from Mahidere Tsibeb

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading

Design a site like this with WordPress.com
Get started